EthioGreen LLC is a registered import / export company located in Washington, DC
202-558-8337
EthioGreen
President Obama Explains Healthcare

President Obama Explains Healthcare.gov
Ethiopian Political Parties
Ethiopian Political Parties
Categories

Ethiopian Television ETV Satellite Frequency
Struggle Over the Nile – Tension and suspicion

ግንቦት 20 ቀን 2003 ዓ.ም. በተካሄደው የድጋፍ ሰላማዊ ሠልፍ ያልተገኙ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ሠራተኞች በሦስት ቀን ውስጥ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ታዘዙ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የሰው ኃይል አስተዳደር ደጋፊ የሥራ ሒደት መሪ ስምና ፊርማ አርፎበት ግንቦት 22 ቀን 2003 ዓ.ም. በመሥሪያ ቤቱ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በተለጠፈው ማስታወቂያ ላይ እንደተገለጸው፣ ግንቦት 20 ቀን በተደረገው አገር አቀፍ ጥሪ ያልተገኙ ሠራተኞች ያልተገኙበትን ምክንያት የሚገልጽ ማስረጃ በሦስት ቀን ውስጥ ማቅረብ አለባቸው፡፡
በድጋፉ ሰላማዊ ሠልፍ ላይ የተገኙ 79 ሠራተኞች ሙሉ ስም ከማስታወቂያው በታች የተዘረዘረ ሲሆን፣ የሰው ኃይል አስተዳደር ደጋፊ የሥራ ሒደት በዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤቱ ስም በሠልፉ ለተገኙ ለእነዚህ ሠራተኞች ያለውን የላቀ አክብሮት ገልጿል፡፡በመሥሪያ ቤቱ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ የተጻፈው ማስታወቂያ እንዲህ ይላል፡፡ ‹‹መሥሪያ ቤታችን ግንቦት 20 ቀን 2003 ዓ.ም. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታን አስመልክቶ በተደረገው የድጋፍ ሰላማዊ ሠልፍ ላይ ጥሪያችንን አክብራችሁ የተገኛችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረው የመሥሪያ ቤታችን ሠራተኞች አገራዊ ግዴታችሁን በመወጣታችሁ የላቀ አክብሮታችንን እየገለጽን፣ የሰው ኃይል አስተዳደር ደጋፊ የሥራ ሒደት በመሥሪያ ቤቱ ስም ከፍተኛ ምስጋናችንን እያቀረብን ከዚህ በታች ስማችሁ ያልተጠቀሰው ሠራተኞች ግን በዕለቱ በተደረገው አገር አቀፋዊ ጥሪ ያልተገኛችሁበትን ምክንያት በሦስት ቀን ውስጥ ማስረጃ ይዛችሁ እንድታቀርቡ እናሳስባለን፡፡››ግንቦት 20 ቀን በተካሄደው ሰላማዊ ሠልፍ ያልተገኙ ሠራተኞች ሪፖርት እንዲያደርጉ የተጠየቁበትን ምክንያት እንዲያብራሩልን የጠየቅናቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ኦዲተር ጄነራል ወይዘሮ አባይነሽ ገብረ መድህን እንደገለጹት፣ በሰላማዊ ሠልፉ ላይ ያልተገኙበትን ምክንያት እንዲያሳውቁ የተጠየቁት ጉዳዩ ከሥራ ዲሲፕሊን ጋር የሚገናኝ በመሆኑ ነው፡፡

Leave a Reply

You must be logged in to post a comment.

Making a donation to Aend-Ethiopia radio station
ON AIR WUST 1120 AM Sunday 3PM - 4PM
Thank you for your donation.

Pulpit rock
Aend-Ethiopia Radio Address (Ethiopian 4th General Election 2010)

ESFNA 2010 SJ, CA
ESFNA
June 2011
S M T W T F S
« May   Jul »
 1234
567891011
12131415161718
19202122232425
2627282930